Skip to main content
04

ክልሉ ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ በልዩ ትኩረት አቅዶ እየሰራ ነው፦ ዶክተር አባስ መሀመድ 
 

የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ 2018 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ማጠቃለያ ግምገማና 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት ምዕራፍ ላይ ከዞንና ከልዩ ወረዳ የመዋቅር አመራሮች ጋር በጋራ በመሆን በቡታጅራ ከተማ ተወያይቷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አባስ መሀመድ በርካታ ኢንቨስተሮች ወደ ክልሉ መጥተው እንዲያለሙ የለማ ኢንዱስትሪ መሬት አዘጋጅቶ በፍጥነት ማስተላለፍ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

ክልሉ ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ በልዩ ትኩረት አቅዶ እየሰራ ነው ብለዋል።

2019 በጀት ዓመት ዕቅዳችን በላቀ ሁኔታ መፈጸም፣ ከቦታ ቦታ ያለውን የአፈጻጸም ልዩነት ማጥበብ፣ የማስፈጸም አቅም ለይቶ መገንባትና ልዩ ድጋፍ መስጠት እንደሚገባም ቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል 

የመድረኩ ተሳታፊዎችም የአፈጻጸም ግምገማውንና በዕቅድ ዝግጅት ያላቸውን የተለያዩ አስተያየቶች ሰጥተዋል።

ኢንቨስትመንትን መሳብ የምንችለው የለማ መሬት ማዘጋጀት ስንችል ነው ያሉት ተሳታፊዎች ቢሮክራሲን ማሳጠር የሚችል የአሰራር ስርዓት መፈጠር አለበት ሲሉም ተናግረዋል 

ለኢንቨስትመንት መሬት ወስዶና አጥሮ በሚይዙ ኢንቨስተሮች ላይ የተጠናከረ እርምጃ በመውሰድ መሬቱን ወደ መሬት ባንክ ማስገባትና ለአልሚ ኢንቨስትመንቶች ማስተላለፍ ይገባል ብለዋል።

ኢንቨስተሮችም ግዴታቸውን በመወጣት የስራ ዕድል መፍጠርና የቴክኖሎጅ ሽግግር ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ሲሉም ተናግረዋል።

በክልሉ የሚመጡ ኢንቨስተሮችም የአካባቢ ተወላጆች ብቻም ሳይሆን የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የሚያጎለብቱና የማህበራዊ ትስስሩን የሚያጠናክሩ ለሌሎች አልሚዎችም ክፍት መሆኑን ገልጸዋል።

በአንዳንድ አካባቢዎች መሬት ለማስተላለፍ በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እንደሚያጋጥማቸው ጠቁመው መሰል ችግሮች በሚፈጠሩባቸው አካባቢዎች ሌሎች አልሚዎች እንዳይገቡ የሚያደርግ በመሆኑ ክልሉ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። 

መሰረተ ልማቶችን ያሟላ የለማ መሬት ለማቅረብ የሚያጋጥመውን የበጀት ችግር ለመቅረፍ መዋቅሮች ልዩ ትኩረት መስጠት አለባቸው ያሉት ተሳታፊዎቹ ክልሉ ልዩ አቅጣጫ ሊያስቀምጥ ይገባል ነው ያሉት።