Skip to main content

ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩል


  •     በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር የሚያስችሉ የፖሊሲና የአፈጻጸም እርምጃዎችን ያመነጫል፣ አግባብ ባለው አካል ሲጸቀድም ተግባራዊ ያደርጋል፣

  •     በክልሉ ውስጥ የሚገኘውን የሀብት ክምችትና የኢንቨስትመንት አማራጭ ዕድሎች መረጃ ከሚመለከታቸው አካላት ይሰበስባል፣ ይተነትናል፣ ያሰራጫል፣ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ፕሮፋይሎችን ያዘጋጃል፣ ለሚመለከተው አካል ያቀርባል፣ ተግባራዊነቱን ይከታተላል፣

  •     ለኢንቨስትመንት የተለየ መሬት ተረክቦ በመሬት ባንክ ይይዛል፣ በመስተዳድር ምክር ቤቱ  ሲፈቀድ መስፈርቱን ለሚያሟሉ ባለሀብቶች በኢንቨስትመንት ሕግ አግባብ ያስተላልፋል፣

  •     የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ሲቀርቡ አግባብ ባለው ሕግ መሰረት ገምግሞ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ይሰጣል፣ ያድሳል፣ ይለውጣል፣ ይሰርዛል፣ የኢንቨስትመንት ስምምነቶችና ማሻሻያዎች መዝግቦ ይይዛል

  •     ለኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ቅልጥፍና የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ይዘረጋል፣ ያደራጃል፣ ያጠናክራል

  •     አግባብ ባለው የኢንቨስትመንት ሕግ መሰረት በኢንቨስትመንት ለተሰማሩ ባለሀብቶች የተፈቀዱላቸውን ማበረታቻዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋል፣ 

  •     ኢንዱስትሪዎች የድጋፍ ፓኬጅ ያዘጋጃል፣ ያቀናጃል፣ ያስፈጽማል በስራ ላይ መዋሉን ይከታተላል፣

  •     ኢንዱስትሪዎች ላይ ያሉ ምርጥ ተሞክሮዎችን በጥናት ለይቶ በማቀናጀት እዲስፋፉ ያደርጋል፤ ተመሳሳይነት ያላቸውን ትስስር እንዲኖር ይሰራል፣

  •     ለኢንዱስትሪ ልማት የሚውሉ የክልሉ የመሬትና የተፈጥሮ ሀብት ላይ ከሚመለከተው አካል ጋር ጥናት ያካሄዳል፡ የጥናቱ ውጤት ለሚመለከተው አካል ያቀርባል፡ ሲጸድቅ በስራ ላይ ያውላል፣

  •     ኢንዱስትሪ መንደሮች፣ ሼዶች፣ ፓርኮች እና ክላስተሮች እንዲስፋፉ፣ እንዲጠናከሩ ያደርጋል፣ አስፈላጊውን ቁጥጥር ያደርጋል፣ 

  •     የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ተደራሽነት እና ምርታማነት ለማጠናከር ከሚመለከተው አካል ጋር ይሰራል፣ መካከለኛ ስልጠና ያለው የሰው ኃይል እንዲያገኙ ያመቻቻል፣

  •     በክልሉ ውስጥ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ስርጭት ተመጣጣኝ እና ባላቸው የልማት እድሎች ላይ የተመሠረቱ እንዲሆን ከሚመለከተው አካል ጋር ይሰራል፣ ለኢንዱስትሪው አከባቢ ማህበረሰብ ውጤታማ መሆናቸውን ያረጋግጣል፣

  •     የማኑፋክቸሪንግ ምርቶችን ወደ ውጪ በመላክ ላይ ለተሰማሩ ፋብሪካዎች እና ኢንተርኘራይዞች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ምርታቸውን ለውጭ ሀገር እንዲያቀርቡ ያግዛል፣

  •     የኢንዱስትሪ የሙያ ብቃት መመዘኛ ህጎችን በስራ ላይ ያውላል፣ የጥራትን እና የምርቶችን ስታንዳርድ ከሚመለከተው አካላት ጋር በመሆን በምስክር ወረቀት ያረጋግጣል ፣ የምርት ጥራት ደረጃ እንዲያገኙ ይሰራል፣

  •     የኢትዮጲያዊያንና ትውልደ ኢትዮጲያውያን ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ይደግፋል፣ ያበረታታል፣ያስተባብራል፣ አፈጻጸማቸውን ይገመግማል፣ በሪፖርት ለሚመለከተው አካል ያሳውቃል፤
  •     ዓላማውን ለማስፈጸም የሚችሉ ሌሎች ተዛማጅ ተግባራትን ያከናውናል፣