Skip to main content

መግቢያ

በሀገርም ሆነ በክልል ደረጃ የግሉ ኢንቨስትመንት ዘርፍ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል፡፡ ይህ ዘርፍ የበለጠ ውጤታማ መሆን ይችል ዘንድ በፌደራል እና በክልል መንግስታት  የተለያዩ አበረታች ዕርምጃዎች ሲወስዱ ቆይተዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር በክልሎችም በርካታ ተግባራት እየተተገበሩ ይገኛሉ፡፡ በቅርቡ በአዲስነት ከተዋቀሩ ክልሎች መካከል አንዱ የሆነው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በቀደመው አደረጃጀት ያገኛቸውን ጠንካራ ጎኖች አጠናክሮ በማስቀጠል ስራውን ለማከናወን ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ ለዚህም ይረዳ ዘንድ የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ በክልሉ የተለያዩ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች የሚገኙ እምቅ ሀብቶችን፤ የኢንቨስትመንት አማራጭ ዕድሎችን፣ እና በህግ አግባብ የተፈቀዱ የቀረጥ ነጻ፣  የገቢ ግብር እፎይታ እና ልዩ ልዩ ማበረታቻዎች አሰጣጥ ያካተተ የኢንቨስትመንት ፖቴንሺያል ጋይድ ቡክሌት አዘጋጅቶ አቅርቧል፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አጠቃላይ ገፅታ

የማዕክላዊ ኢትዮጵያ ክልል በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት በአዋጅቁጥር 1/1987 ዓም አንቀጽ 47 መሠረት ከተመሰረቱት ክልሎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ክልሉ የሚገኘዉ በኢትዮጵያ ማዕከላዊ አቅጣጫ ሲሆን ብዝሃ ማዕከላትእንዲኖሩት ተደርጎ የተዋቀረ ሲሆን የመስተዳድር ምክር ቤት መቀመጫው ሆሳዕና ከተማ ነው፡፡የክልሉ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ 7004’ እስከ 8003’ ሰሜናዊ ኬክሮስ እና 37020’ እስከ 38060’ ምሥራቃዊ ኬንትሮሰ ላይ ነው፡፡ አዋሳኞቹም በሰሜን፣ በምእራብና በምስራቅ አቅጣጫ  ከኦሮሚያ ክልል፤ በደቡብ በኩል ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ በደቡብ ምዕራብ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ይዋሰናል፡፡ አስተዳደራዊ መዋቅሩም በዞኖች፣ በልዩ ወረዳዎች፣ በወረዳዎች፣ በከተማ አስተዳደሮችና በቀበሌዎች የተደራጀ ነው ክልሉ1,515,.600 /ርስፋት ያለው ሲሆን ከአጠቃላይ የኢትዮጵያ የቆዳ ስፋት1.38 በመቶውን የሚይዝ ነው፡፡ የሕዝብ ብዛት በተመለከተ 1999 ..የብሔራዊ የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት መረጃ ፕሮጀክሽን መሠረት የክልሉ የሕዝብ አማካይ አመታዊ ዕድገት ምጣኔ 2.9 በመቶ ነው። የሕዝብ ዕድገት ምጣኔ በመኖሪያ አካባቢ በተመለከተ የገጠር ሕዝብ አመታዊ ዕድገት 2.8 በመቶ ሲሆን በከተማ የሕዝብ የዕድገት ምጣኔ 4.8 በመቶ ነዉ  በዚህ መሰረት 2015 .የክልሉ ሕዝብ 7,039,772 እንደሆነ  ይገመታል፡፡ ከዚህ ውስጥ 80.7% በገጠር እና ቀሪው 19.3 % በከተሞች የሚኖር ነው፡፡ ይህም ከአገሪቱ አጠቃላይ ህዝብ 6.47 በመቶውን የሚሸፍን ሲሆን የክልሉ አማካይ የህዝብ ጥግግት ደግሞ 464 ሰዎች በአንድ ካሬ .ሜነው።ክልሉ በአሁኑ ወቅት ዞኖች፣ 3 ልዩ ወረዳዎች፣ 50 ወረዳዎች እና 29 የከተማ አስተዳደሮች የተከፈለ ነው። ክልሉ 1294 ቀበሌዎች ያሉት ሲሆን ከነዚህም 185 የከተማ 1109 የገጠር ቀበሌያት ናቸው፡፡የክልሉን ስነምህዳር በተመለከተ የማዕከላዊ የኢትዮጵያ ክልል በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን ሁሉንም የአየር ንብረቶች ይዟል በሚባል ደረጃ ለኑሮ ምቹ የሆኑ የደጋ፣ የወይና ደጋ እና የቆላ አከባቢዎች ያሉት ሲሆን በሁለት የተራራቁ ጫፎች ያለው የአየር ንብረትም በክልሉ የተለያዩ ስነምህዳር (ecology) የተፈጥሮ ሀብቶች፣ የተለያዩ የግብርና ሥርዓቶች፣  የአኗኗርና የባህል  ብዝሀነት እንዲኖር አድርጓል፡፡ የክልሉ ከፍተኛ ሥፍዎች እንደ ዘቢዳር፣ሙጎ አምባሪቾና ሸንቆላ የመሳሰሉ ተራራዎች ሲሆኑ ዝቅተኛው ሥፍራ ደግሞ በጠምባሮ ልዩ ወረዳ በኦሞ ወንዝ አቅራቢያ ባለው የኦሞ ሸለቆ  ጫፍ ከባህር ጠለል በላይ 447 ሜትር ከፍታ ያለው ሥፍራ ነው፡፡ 

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ መሰረቶች

የግብርና ውጤቶች፡

የክልሉ ብሔረሰቦች ዋነኛ የኢኮኖሚ መሰረት ብዝሀነት ያለው የግብርና ሥርዓት (diversified agricultural systems) ነው፡፡ በክልሉ የግብርና ሥርዓት ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው  የእርሻ ሥራ  ሲሆን የእንስሳት እርባታም ጎን ለጎንይካሄዳል፡፡ በክልሉ በዋነኛነት የሚመረቱ የብርዕና አገደ ሰብሎች (በቆሎ፣ስንዴ፣ ገብስ፣ ጤፍጥራጥሬዎች (አተር፣ ባቄላ፣ ሽምብራ)  የተለያዩ ፍራፍሬዎች (ሙዝ፣ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ አፕል፣ አናናስ) የስራ ስር ሰብሎች (እንሰት፣ድንች፣ ጎደሬ)፣እንዲሁም ቡና፤ ዝንጅብል እና የተለያዩ ቅመማ-ቅመሞች ወዘተ ናቸው፡፡  የጤና ተቋማትና አገልግሎቶች 2014 .ምየክልሉ ጤና ሽፋን 79% ሲሆን ግንባታቸዉ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት የጀመሩ አዳዲስ ተቋማትን ጨምሮ በክልሉ በአጠቃላይ 24  ሆስፒታሎች፣  216 ጤና ጣቢያዎች፣ 1178 ጤና ኬላዎችና 272 ክሊኒኮች (ሁሉም ዓይነትይገኛሉ። 

የትምህርት ተደራሽነት   
2014 .ምበክልሉ መንግስት የሚተዳደሩ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች(1-8) በጥቅሉ 1750፣የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች (9-12) 260 እና ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች 6፣የቴክኒክና ሙያ ትም/ናሥልጠና ኮሌጆች 27 የደረስ ሲሆን፤ መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች የሚተዳደሩ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች(1-8) 213 እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ደግሞ (9-12) 22 የግል ትም/ ሥልጠና ኮሌጆች 30 የመምህራን ትም/ኮሌጅ አንድ 1 ጤና ኮሌጅ አንድ ናቸው::  ከዚህም በተጨማሪ በመንግስት የሚተዳደሩ ከከፍተኛ  ትምህርት ተቋማት አንጻር ሦስት ዩኒቨርሲቲዎችና ካምፓሶች ይገኛሉ፡፡ 

የመንገድ መሰረተ ልማት ሽፋን፡   
በክልሉ እስከ 2014 .ምግንባታዉ ተጠናቅቆ ርክክብ የተደረገ ክልላዊ ጥቅል የመንገድ መሰረተ ልማት ሽፋን 4983.25 .ሜሲሆን ይህም 2028 .ሜበደቡብ መንገዶች ባለስልጣን፣ 1791.9 . በትራንሰፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የሁ/አቀ////ፕ፣ 699.4 . የአስፓልት መንገድ እና ቀሪው 464 . የጠጠር መንገድ በፌደራል መንገዶች ባለስልጣን  የተገነባ  ነው፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት ክልላዊ ከሁሉ አቀፍ የገጠር ተድራሽ መንገድ ውጭ ክልላዊ የመንገድ ጥግግት 210.06 ./1000] ካሬ ..ሜመሆኑን ማወቅ ይቻላል፡፡ 


የከርሰ ምድር ማእድን እና የኮንስትራክሽን ግብአት እምቅ ሀብት   
የከርሰ ምድር የማዕድን ሃብትን በተመለከተ ሀገር አቀፍ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መረጃ እና የተፋሰስ የማስተር ፕላን ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የከርሰ እና የገጸ ምድር ማዕድን ክምችት መኖሩ ተለይቷል፡፡ ለኢንዱስትሪ ክፍለ ኢኮኖሚ ሊውሉ የሚችሉ እንደ ክሌይ፣ የድንጋይ ከሰል፣ የብረት ማዕድን ፣የጌጣ ጌጥና የግንባታ ማዕድናት ይገኛሉ፡፡ ጉራጌ፣  ሃዲያ  እና የም ዞን ካኦላይን፣ ላይም ስቶን ደግሞ በጉራጌ ዞን የሚገኝ ሲሆን መጠናቸውም ወደ ኢንዱስትሪ ሰኬል መግባት የሚያስችል እንደሆነ መረጃው ያመለክታል፡፡አሸዋ፣ ጥርብ ድንጋይ፤ የኖራ ድንጋይ እና የመሳሰሉት የኮንስትራክሽን ግብአቶች በክልሉ በተለያዩአከባቢዎች በስፋት ይገኛሉ፡፡ ከዚህም ባሻገር በኮንስትራክሽን ሙያ ዘርፍ የረጅም ጊዜ ልምድና እውቀት ያላቸው፤  በቁጥራቸውም እጅግ ብዛት ያላቸው ሙያተኞች የሚገኙበት ክልል በመሆኑ የኮንስትራክሽን ሥራ ለማከናወን በእጅጉ አመቺ ነው፡፡ የድንጋይ ከሰል ከፍተኛ የሀይል ፍጆታ ለሚፈልጉ ለብረታ  ብረት፣ ለስሚንቶና ለሴራሚክስ ኢንዱስትሪ ዋና የሀይል ምንጭ ሆኖ ስለሚያገለግል ለኢንዱስትሪ ልማቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡ 

የመስኖና እና ንጹህ የመጠጥ ውሀ አቅርቦት   
ከመስኖ አቅም አኳያ በአነስተኛ ግድብ /Micro and Min Dams/ ሊለሙ የሚችሉ ወንዞች፤ በሃዲያ ዞን አመካ፣ ገሙና፤ እና ጎምቦራ ወንዞች፣ በጉራጌ ዞን ዊንቄ፣ ዋቤ፤ አንዘቻ፤ ደጎሰ ወራቤሳ፣ ዳጌ፤ጎግዋሬ እና ዋልጋ ወንዞች፤ በሀላባ ዞን የሚገኘው የብላቴ ወንዝ በሰልጤ ዞን የሚገኘው የዲጆ ወንዝ እንዲሁም የጊቤ ወንዝ አቅም ያላቸው ተጠቃሽ የክልሉ ሀብቶች ናቸው፡፡ ከመጠጥ 4 ውሀ አቅርቦት አንጻር 2014 .ምበተካሄደው የንጹህ የመጠጥ ውሃ ተቋማት ቆጠራ እና የአቅርቦት ሽፋን ጥናት መሰረት ክልላዊ አማካይ የንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ሽፋን 49% ደርሷል፡፡

የኃይል አቅርቦትን በተመለከተ   
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም የተገነቡና በመገንባት ላይ ያለን ጨምሮ አምሰት የኃይል ማስተላለፊያ ሳብስቴሽን ያሉት ሲሆን በአገልግሎት በግብርና በተለይም በኢንዳስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ግል ባለሁብቶች የማያቋርጥ የኃይል አቅርቦት የሚቀርብበት በመሆኑየክልሉ የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነት ከሌሎች አከባቢ በተለየ ሁኔታ ከፍ ያደርገዋል፡፡ ክልሉ ለኢንዱስትሪዎች  የሃይል  ምንጭ ከሚሆኑት ዘመናዊ የሃይል ምንጮች ኤሌክትሪክ አንዱ ሲሆን የኤሌትሪክ አገልግሎት ክልላዊ ስርጭቶች /ICS/ እርስ በርስ በተያያዙ ሲስተም ተዘርግተዋል። (የመረጃው ምንጭ ፕላን ቢሮ

የክልሉ ሰው ኃይል ለኢንቨስትመንት ያለው ምቹ ሁኔታ   
በየትኛውም የኢንቨስትመንት ዘርፍ ተቀጥረው መስራት የሚችሉ ከፍተኛና መካከለኛ ሙያ ያላቸው ዜጎች በማያቋርጥ ሁኔታ እያፈራ ያለ ክልል በመሆኑ ለየትኛውም የኢንቨስትመንት ዘርፍ የሚሆን የሰው ኃይል ፍላጎት በቀላሉ ማግኘት የሚቻልበት ክልል ነው፡፡ከዚህም በተጨማሪ የክልሉ ተወላጅ ዜጎች ልዩ መለያ የሆነው ሥራ ወዳድነት እና ታታሪነት እንዲሁም የሀገር ውስጥ የሰው  ኃይል ፍላጎትን ማሟላት እንደተጠበቀ ሆኖ በተለያዩ የአለም ሀገራትና በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከየትኛውም አከባቢ በተለየ ሁኔታ ተንቀሳቅሰው የሚሰሩ በመሆናቸው በክልሉ ውስጥ በየትኛውም የኢንቨስትመንት ዘርፍ በግብርና በተለይም በኢንዳስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ የግል ባለሀብቶች ምርቶቻቸውን በቀላሉ በውጭና በሀገር ውስጥ ገበያዎች ለመሽጥ የሚያስችላቸው ልዩ እድል ያለበት ክልል ነው፡፡