Skip to main content

የመዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ተቋማዊ ዳራ 

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ክልሉ የአስፈጻሚ ቢሮዎችን ማቁቋሚያ፣ ስልጣን እና ተግባርን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 199/2015 መሰረት የተቁቋመ መንግስታዊ ተቋም ነው ቢሮው በክልል ደረጃ በሁለት ዘርፎች እና በስድስት የወል ዳይሬክቶሬቶች የተዋቀረ ሲሆን የወል ዳይሬክቶሬቶችም እንደ ስራው አስፈላጊነት ተደራጅተው ተግባራቸውን ሲወጡ ቆይተዋል በክልሉ በሚገኙ ሁሉም ዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች የኢንቨስትመንትና ኢንዱስተሪ ልማት መዋቅሮች ተደራጅተው ከቢሮው ጋር በመቀናጀት ተግባራቸውን እየተወጡ ይገኛሉቢሮው በአዲሱ ክልል በአዋጅ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ እንዲሁም በቀድሞ የደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ/ ስር በነበረበት ጊዜ የኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ልማትን በማስፋፋት የክልሉን ህብረተሰብ ከዘርፉ ተጠቃሚ ለማድረግ በሰፊዉ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። እንዲሁም በከተሞች የመሰረተ ልማት በተሟሉባቸው አካባቢዎች የኢንዱስትሪ እና የአገልግሎት ሰጪ ሴክተሮች ተጠናክረው  ኢንዲስፋፉ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካለትና ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ስራ ለመስራት እንቅስቃሴ ተደርጓል። በተለይ በክልሉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በተስፋፉባቸው አካባቢዎች በርካታ ዜጎች የስራ ዕድል፣ የቴክኖሎጂ እና የክህሎት ተጠቃሚ ሆነዋል እንዲሁም ለክልሉ ወደ ስራ የተሰማሩ ባለሃብቶች መንግስት ገቢ ግብር በመክፈል እና ተኪ ምርቶችን በማምረት ለክልሉ ብሎም ለሃገሪቱ ኢኮኖሚ እድገት የድርሻቸውን ሲወጡ ቆይተዋል ባጠቃላይ ቢሮው እነዚህንና መሰል ግቦችን በማሳካት በአዋጅ የተሰጡትን ተግባራት በአግባቡ በማከናወን የተሰጠውን ሃላፊነት እየተወጣ ዛሬ ላይ ደርሷል